More

    ቤተክርስቲያን የማፍረስ ዘመቻ በድሬደዋ

    on

    |

    views

    and

    comments

    ባለፈው ሳምንት በድሬደዋ መካነ እየሱስ ቤተክርስቲያን እና በከተማ ከንቲባ ጽ/ቤቱ መካከል ተፈጥሮ የነበረው ችግር በውይይት መፈታቱን ቤተክርስቲያኗ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግራለች፡፡
    ቤተክርስቲያኗ ትፍረስ በሚል ላወጣው ደብዳቤም የከንቲባ ጸ/ቤቱ ቤተክርስቲያኗን ይቅርታ መጠየቁን እና ሁሉም ነገር በንግግር እንደሚፈታ መናገሩን አስታውቃለች፡፡

    በተደረገው ንግግርም ቤተክርስቲኗ የያዘችውን ይዞታ ማልማት ከቻለች በቦታው እንድትቀጥል ካልሆነ ግን የከንቲባ ጸ/ቤቱ ተለዋጭ ቦታ ላይ የምትክ ቤት ሰርቶ እንደሚሰጥ ቃል መግባቱን የቤተክርስቲያኗ ሰብሳቢ አቶ በለሳቸው አምባሮ ለጣቢያችን ተናግረዋል፡፡
    ከቦታው ተነስቶ ወደ ተለዋጭ ቦታ መሄዱም ቢሆን ከቤተክርስቲያኗ መሪዎች ጋር በመነጋገር ብቻ እንደሆነ መተማመን ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል፡፡

    ቀደም ሲል የተላከው ደብዳቤም ቤተክርስቲያነኗ ዙሪያ ላይ ላሉ ተቋማት የተዘጋጀ መሆኑን ከንቲባው መናገራቸውን የገለጹት የቤተክርስቲኗ ሰብሳቢ ይቅርታ መጠየቃቸውንም አነስተዋል፡፡
    ስለሆነም ከተቀመጡት ሁለት አማራጮች መካከል ቤተክርስቲያኗ የፈለገችውን መምረጥ እንደምትችል የከንቲባ ጸ/ቤቱ ገልጿል፡፡

    በሚቀጥለው ሰኞ ከድሬደዋ ከንቲባ ጋር ለመነጋገር ዋናው ሲኖዶስ ከአዲስ አበባ ወደ ድሬደዋ እንደሚያመራ የተገለጸ ሲሆን ከሚደረገው ሰፊ ውይይት በኋላ ቤተክርስቲያኗ የሚበጃትን ትምርጣለች ብለዋል፡፡

    በመጨረሻም የከተማ ከንቲባ ጽ/ቤቱ ጥፋቱን አምኖ ይቅርታ መጠየቅ በመቻሉ ቤተክርስቲያኗ በጣም እንደምታመሰግን የቤተክርስቲያኗ ሰብሳቢ አቶ በላቸው አምባሮ አስታውቀዋል፡፡

    Share this
    Tags

    Must-read

    Nathaniel was born and raised in Adigrat, Tigray region, known for its white honey production

    Nathaniel was born and raised in Adigrat, Tigray region, known for its white honey production. He graduated from Addis Ababa University of Science and Technology...

    Mr. Nigussu Tilahun’s house was searched By Government Police

    He was the spokesperson of the Prime Minister. They met every day at the Four Kilo Palace. It is said that they used to...

    Ethio Telecom announced four services

    Ethio Telecom announced four services Ethio Telecom has introduced services to its customers today that allow for better voice and video quality phone calls. The announced...
    spot_img

    Recent articles

    More like this

    LEAVE A REPLY

    Please enter your comment!
    Please enter your name here